በአማራ ክልል በወሎ መርሳ ከተማ የሚኖሩ ሙስሊሞች ከአስር ሰላት ቡሀላ መንግስት በሙስሊሞች ላይ እያደረሰ ያለዉን የመብት ረገጣና በከተማቸዉ ሊዘጋጅ የነበረዉን የአንድነትና የሰደቃ ፕሮግራም መንግስት በማገዱ አደባባይ በመዉጣት የከተማዎ ሙስሊሞች ተቃዉሟቸዉን ሲያሰሙ ከአካባቢዉ የፌደራል ፖሊሶች ጋር መጋጨታቸዉ ተሰማ:: በዚህም ግጭት የፌደራል ፖሊስ በወሰደዉ የሀይል እርምጃ በርካቶች በከፍተኛ ደረጃ ድብደባ እንደተፈፀመባቸዉ የአካባቢዉ ምንጮች ገለፁ:: በርካታ ሙስሊም ሴቶችና ወንዶችም ወደ ወልዲያ ከተማ ተወስደዉ መታሰራቸዉን ምንጮቻችን ገልፀዎል:: አላህ ይድረስላቸዉ!!!
አማራ ክልል ወሎ መርሳ ከተማ
23
Apr